የሲ.ፒ.ጄ የጥንቃቄ ምክሮች ፤ ስለ ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ አዘጋገብ

ራስን ለመከላከል የሚያስችሉ መሳሪያ ያደረጉ ሜክሲካዊ ጋዜጠኞች፣ ሜክሲኮ ከተማ በሚገኘው ባልቡየና አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ፣ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት፣ ሚያዚያ 8፣ 2012 ዓ.ም ያስተዳደር ሰራተኞች ያሰሙት የነበረውን ተቃውሞ ሲዘግቡ የሚያሳይ ምስል (ኤ.ፍ.ፒ/ፓድሮ)::

ግንቦት 12፣ 2013 ዓ.ም የተሻሽለ 

የዓለም የጤና ድርጅት ኮቪድ-19(ኖቭል ኮሮናቫይረስ) ዓለማቀፍ ወረርሽኝ መሆኑን መጋቢት 2፣ 2012 ዓ.ም. አስታውቋል፡፡ የዓለማቀፉ ሁኔታ እየተሻሻለ በመጣ ቁጥር፣ ሀገራት፣ የጉዞ እቀባቸውን እና ሲውስዱ የነበሯቸውን የጥንቃቄ እርምጃዎች እያላሉ ወይም እያለዘቡ መጥተዋል። ይህም የሆነው፣ የተለያዩ የዜና ዘገባዎች እንደሚያሳዩት፣ አዳዲስና ለየት ያሉ የኮሮና ቫይረሶች መገኘታቸውን እና የኮቪድ-19 ክትባት መረሃ-ግብር መጠናክርን ተከትሎ ነው። 

ሕዝብ ስለቫይረሱ ሊኖረው የሚገባውን ግንዛቤ በማስጨበጥና መንግስታት ቫይረሱን ለመዋጋት የሚደረጉትን ጥረቶች በማሳወቅ ረገድ፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ጋዜጠኞች ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ ነው። በሲ.ፒ. ጄ እንደተዘገበው፣ ጋዜጠኞች ይህንን የሚያደርጉት፣ በብዙ ሀገራት ያሉ መንግስታት፣ በነፃነት የመዘገብንና መረጃ የማግኘትን ሂደት በሚያሰናክሉበት ሁኔታ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር፣ የሚዲያው አካላት፣ ከፍተኛ ጫናና ችግር እየገጠማቸው ነው፡፡ በዚህም የተነሳ፣ ከጋዜጠኞች ጋር በሲ.ፒ. ጄ የተደረጉ ቃለ መጠይቆች እንደሚሳዩት፣የመገናኛ ብዙኃን አባላት፣ ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀሱ፣ ቃለ መጠይቅ ሲያደርጉና ስራቸውን በሚሰሩበት ቦታ በከፍተኛ ደረጃ ለቫይረሱ ተጋላጭ እየሆኑ ነው:: በቅርቡ የወጣው የሲ.ፒ.ጄ ሪፖርት እንደሚያሳየው፣  ጋዜጠኞች የሳንሱር ችግር ገጥሟቸዋል፤ ለእስር ተዳርገዋል፤ በኮቪድ 19 የተነሳ መተዳደሪያቸውን አጥተዋል።

እራሳችንን በየጊዜው ከሚወጡ ምክሮችና ክልከላዎች ለማስተዋወቅ/ለማዘመን፣ እኛ ሰለወረርሽኙ የምንዘግብ ጋዜጠኞች የዓለማቀፉ የጤና ደርጅት እና የየአካባቢያችን የጤና አካላት የሚያወጧቸውን መረጃዎች በአንክሮ ልንከታተል ይገባል። 

የአሜሪካው የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (ሲ.ዲ.ሲ) እንዳስገነዘበው፣ ክትባት የወሰዱ የሚዲያ ሰራተኞችም ቫይረሱን ሊያስተላልፉ እንደሚችሉ ልብ ሊሉ ይገባል፤ የል ሜዲሲን እንደሚለውም፣ የተለያዩ ክትባቶች፣ የተለያዩ የቫይረሶችን ለመከካላከል ያላቸው አቅም ይለያያል። ስለሆነም፣ ከኮቪድ-19 ጋር የተያያዙ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ እና የአፍና-አፍንጫ መልበስ ያሉ የጥንቃቄ እርምጃዎች እንደቀጠሉ ሊቆዩ ይገባል። 

በተጨማሪም፤ እኛ ሰለወረርሽኙ የምንዘግብ ጋዜጠኞች፣ የጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስ የመረጃ ማዕከል፣ ስለአሁናዊ የቫይረሱ ስርጭት ለማወቅ አስተማማኝ ምንጭ መሆኑን ማወቅ ጠቃሚ ነው።

በመስክ ስራ ላይ እራስን ከአደጋ ጠብቆ ስለመቆየት

የዓለማቀፍ የጉዞ እገዳዎች እና የጥንቃቄ-ነክ እርምጃዎች በየጊዜው ይቀያየራሉ፡፡ ያለበቂ ወይም ያለምንም ማሳሰቢያ፣ የዘገባ ስራዎች ሊለወጡ ወይም ሙሉ በሙሉ ሊሰረዙ ይችላሉ፡፡

ስለዚህ፣የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመዘገብ የሚሹ ባለሙያዎች የሚከተሉትን የጥንቃቄ መረጃዎች ልብ ሊሉ ይገባል፤

ከስራ ሥምሪት በፊት

ስነልቦናዊ ደህንነት

በቫይረሱ መለከፍን እና ቫይረሱን ወደ ሌሎች ማስተላለፍን መከላከል

በአሁኑ ጊዜ፣ በጣም ብዙ ሀገራት፣ ማሕበራዊ/ አካላዊ ርቀትን ተግባራዊ ማድረግ እንደቀጠሉ ናቸው፡፡ ይሁን እንጅ፣ የሚመከረው የርቀት መጠን እንደምንግኝበት ሀገር ሊለያይ ይችላል። ባደጋ ጊዜ አገልግሎት ወደሚሰጥባቸው ወይም ከዚህ በታች ወደ ተገለጹ፣ የስጋቱ መጠን ከፍ ወዳለበቸው፣ ወደሚክተሉት ቦታዎች ሄደን ስለ ቫይረሱ ስንዘግብ፣ በቦታዎቹ ስለሚደረጉ የንጽህና አጠባበቆች በቅድሚያ በቂ ግንዛቤ ሊኖረን ይገባል፡፡ ስለሁኔታው የምንጠራጠር ከሆነ፣ ወደ እነዚህ ቦታዎች መሄድ የለብንም፤

ራሳችንን ከቫይረሱ ለመከላከል የሚያስችሉን መደበኛ ምክረ ሃሳቦች ደግሞ የሚከተሉትን ያካትታሉ፤

ራስን ለመከላከል የሚያገለግሉ የህክምና መሳሪያዎች

የሚዲያ ሠራተኞች፣ የሚዘግቡትን ነገር በጥንቃቄ ለመዘገብ፣ የተሰማሩበትን የስራ ፀባይ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ እራስን ለመከላከል የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን ማድረግ/መልበስ ሊያስፈልጋቸው ይችላል። ራስን ለመከላከል የሚያገለግሉ የህክምና መሳሪያዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፤ ተጠቅመን የምንጥላቸው ጓንቶች፣ የፊት ጭንብሎች፣ የመከላከያ ሽርጦች፣ቱታዎች/በመላ አከላችን የሚጠለቁ ልብሶች እና ተጠቅመን የምንጥላቸው የጫማ መሸፈኛዎች።

እነዚህን ቁሳቁሶች በአግበቡ ለማጥለቅና ለማውለቅ ደግሞ መልካም የጥንቃቄ ተሞክሮዎችና የአጠቃቀም መመሪያዎችን በትክክል መከተልን ይጠይቃል፡፡ በሲ.ዲ.ሲ የተዘጋጀውን አጠቃላይ መመሪያ ለመመልከት ይህንን እንጫን፡፡ ብክለትን ከአንዱ ወደ ሌላው የማስተላለፍ አደጋ ከፍተኛ ስለሆነ፣ እነዚህን መመሪያዎች ከመተግበር ልንዘናጋ አይገባም፡፡ ከተጠራጠርን፣ ወደ ስራ ከመሰማራታችን በፊት የባለሙያ መመሪያ እና ስልጠና እንጠይቅ።

በብዙ ሀገሮች፣ አሁንም ጥራታቸውን የጠበቁ እራሰን ለመከላክል የሚያግለግሉ የህክምና መሳሪያዎች ከፍተኛ የአቅርቦት እጥረት ሊኖር ይችላል፤ መሳሪያዎቹን ማግኘትም አስቸጋሪ ነው። በመሆኑም፣ እነዚህን መሳሪያዎች መጠቀማችን እጥረቱን ሊያባብስው እንድሚችል ልብ እንብል።

የፊትና የአፍንጫ ጭንብሎች

የፊት ጭንብልን ባግባቡ መጠቀም፣ በተለይ ከማህብረሰቡ መካከል ሆነው ከተፋፈጉና በሰው ከተጨናነቁ ወይንም ለቫይረሱ በከፍተኛ ደርጃ ተጋላጭ ከሆኑ ስፍራዎች የሚገኙ የማህብረሰብ አባላትን እያነጋገሩ ለሚዘግቡ የሚዲያ ሰራተኞች በጣም አሰፍላጊ ነው። በተፋፈጉ ስፍራዎች፣ የቫይረሱ ጠብጣዎች መጠን ከሌሎች ቦታውች ከፍ ሊሉ ስለሚችሉ፣ በቫይረሱ የመያዝ እድላችን በከፍተኛ ደረጃ ሊጨምርው እንደሚችል ልብ ልንል ይገባል። 

ባግባቡ ካልተጠቀምንባቸው ፣ የፊት ጭንብሎች በቫይረሱ ለመለከፍ ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ የሚሉ ስጋቶች እንዳሉ ልብ እንበል፡፡ ላንሴት (Lancet) ያደረገው አንድ ጥናት እንደሚያሳየው፣ በቫይረሱ በተጋለጠ አካባቢ የተደረገ የህክምና የፊት ጭንብል፣ ቫይረሱን ለሰባት ቀናት ይዞ ሊቆይ ይችላል፡፡ ይህ ጥናት እንደሚያሳየው፣ ጭንብልን ማድረግ፣ መልሶ መጠቀም ወይንም  ጭንብሉን እንዳደረጉ ፊትን መነካካት ራስን ለቫይረሱ በከፈተኛ ደረጃ ማጋለጥ ማለት ሊሆን ይችላል።

የፊት ጭንብልን የግድ ማድረግ ካለብን ደግሞ፣ የሚከተሉትን ምከሮች መተግበር የግድ ይላል፤

መሳሪያዎችን በጥንቃቄ ስለመያዝ

ኮቪድ 19 በቫይረሱ በተበከሉ መሳሪያዎች አማካኝነት የመዛመት እድሉ እሙን ነው፡፡ ስለሆነም፣ መሳሪያዎቻችንን ማጽዳትና ከጀርሞች ነጻ የማድረግ ልምድ የምንጊዜም ተግባራችን መሆን አለበት፡፡  

የኤሌትሪክ መሳሪያዎችን ስለማጽዳት

የኤሌትሪክ መሳሪያዎችን ለማጽዳት የሚከተሉት ነጥቦች እንደ አጠቃላይ መመሪያ ሊያገለግሉን ይችላሉ። የምንጠቀምበትን አንድን መሳሪያ ለማጽዳት ክመሞከራችን በፊት፣ ሁሌም መሳሪያውን ያመረተው ድርጅት ያዘጋጀውን መመሪያ በሚገባ ማንበብ ይኖርብናል።ሁሌም የኤሌትሪክ መሳሪያዎችንና የኤሌትሪክ ገመዶችን ከሶኬቶች መንቀል/ማላቀቅ አለብን።  

ተጨማሪ ዝርዝር መመሪያዎችን ደግሞ እዚህ መጣጥፍ ዘንድ ማግኘት ይቻላል።

የዲጂታል ደህንነት

ወንጀል እና በሥራ ላይ ስለሚደረግ አካላዊ ጥንቃቄ

የውጭ ጉዞን ያካተቱ ሥራዎች

በመላው ዓለም በተደነገጉ የጉዞ እቀባዎች የተነሳ፣ በአሁኑ ሰዓት የውጭ ጉዞዎች እጅግ እየቀነሱና በጣም አዳጋች እየሆኑ ቀጥለዋል፡፡ 

ሥራችንን ከጨረስን በኋላ

ምልክቶች ሲታዩብን፤

እናድርግ፡፡

የሲ.ፒ.ጄ  የጥንቃቄ “ኪት” ለጋዜጠኞችና ለዜና ሰዎች ስለ አካላዊ፣ ዲጂታላዊ ስነ-ልቦናዊ ጥንቃቄዎች መረጃዎችና ጠቃሚ ምክሮችን ይሰጣል፡፡ ይህ ደግሞ ስለ ምርጫና ሊከሰቱ ስለሚችሉ ህዝባዊ አመጾች ተፈላጊ መረጃን ይጨምራል፡፡

Exit mobile version