ዲጅታል ደህንነት፤ የኢንተርኔት መዘጋት

የካሽሚሪ ጋዜጠኞች በህንድ ቁጥጥር ስር በወደቀችው ካሽሚር፣ ስሪናጋር ክልል የኢንተርኔት አገልግሎት ከተቋረጠ ከ100 ቀናት በኋላ ማለትም ህዳር 2፣ 2012 መፈክሮችን እና ተቃውሞዎችን አሰምተዋል። በአለም ዙሪያ ያሉ ጋዜጠኞች የኢንተርኔት አገልግሎት በሚቋረጥበት ጊዜ ለመስራት ይቸገራሉ፤ የኢንተርኔት መዝጋት ድንጋጌዎች የሚተላለፉት ብዙ ጊዜ በአመጽ ወይም በፖለቲካዊ አለመረጋጋት ወቅት ነው። (ኤፒ ፎቶ/ሙክታር ክሃን)

የኢንተርኔት መዘጋት ለፕሬስ ነፃነት ከባድ መዘዝ እንዳለው እና ጋዜጠኞችንም ስራቸውን በብቃት ለማከናዎን አዳጋች እያደረገባቸው እደሆነ ሲፒጄ አረጋግጧል። ኢንተርኔት ተዘጋ ወይም ተገደበ ማለት፣ የሚዲያ ሰራተኞች አንድ ሁነት እስኪፈጠር ድረስ ምንጮችን ማግኘት፣ የመረጃን እውነታ ፍተሻ ማድረግ ወይም ታሪኮችን መሰነድ አይችሉም ማለት ነው። ኢንተርኔት ሊዘጋ የሚችለው ባብዛኛው በግጭት፣ በፖለቲካ አለመረጋጋት ወይም በምርጫ ወቅቶች ሲሆን፣ እንደ አክሰስ ናው (Access Now) ያሉ አለም አቀፍ ተቆጣጣሪዎች እንደሚሉት፣ መንግስታት እነዚህን አጋጣሚዎች የሚጠቀሙት የህዝቡን የመረጃ ተደራሽነት ለመገደብ ነው።

የተለያዩ የኢንተርኔት መዘጋት ዓይነቶች ያሉ ሲሆን፣ በመላው ሀገር ወይም በተወሰኑ ክልሎች ብቻ ሊከሰቱ ይችላሉ። ሙሉ በሙሉ የመዘጋት ችግር የሚያጋጥማቸው ጋዜጠኞች፣ የኢንተርኔትም ሆነ የስልክ አግልግሎት ሙሉ በሙሉ ይቋረጥባቸዋል፤ ይህም ማለት፣ ኢንተርኔትን መጠቀም፣ ከሌሎች ሰዎች ጋር በመስመር ወይም በተንቀሳቃሽ ስልክ መገናኘት አይችሉም ማለት ነው። መንግስታት፣ የኢንተርኔት አገልግሎት ሰጪዎችን፣ የመገናኛ መተግበሪያዎችን ወይም እንደ ዩቲዩብ ያሉ የተወሰኑ ጣቢያዎችን ወይም አገልግሎቶችን እንዲገድቡ ሊያዟቸው ይችላሉ። እንደዚህ አይነቱን አገልግሎት በከፊል የማቋረጥ ሁኔታ የሚዲያ ሰራተኞችን ከሌሎች ሰዎች ጋር የመገናኘት ወይም ይዘትን ኢንተርኔት ላይ የመጫን አቅምን ይገድባል።

የኢንተርኔት ፍጥነትን በመቀነስ ድረገፆች ይዘታቸውን ማሳየት እንዳይችሉና እና ሰዎች ይዘቶችን መጫን እንዲያቅታቸው በማድረግ ኢንተርኔቱን ጥቅመ-ቢስ ማድረግ ሌላው የኢንተርኔት አገልግሎትን የመቆጣጠሪያ ዘዴ ነው።

ከሁሉም አይነት የኢንተርኔት መዘጋቶች ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመቋቋም፣ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ወሳኝ ጉዳይ ነው። የኢንተርኔት መዘጋት ለሚያሳስባቸው ጋዜጠኞች፣ የሚከተሉት መረጃዎች ጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ።

አጠቃላይ የዲጂታል ደህንነት ምርጥ ተሞክሮ

ስለመሣሪያ ደህንነት እና ስለተመሰጠሩ ግንኙነቶች የበለጠ ለመረዳት የሲፒጄን ዲጂታል የጥንቃቄ ኪት (CPJ Digital Safety Kit) ይመልከቱ። 

የኢንተርኔት መዘጋትን በተመለከት ዝግጅት ማድረግ

ትክክለኛ መሳሪያዎችን ይምረጡ

የመስመር ላይ መሳሪያዎች እና አገልግሎቶች ለደህንነት ጥሰቶች ተጋላጭ ናቸው። በተለይ እንደ የመልዕክት መላላኪያ መተግበሪያዎች ያሉ የመገናኛ መሳሪያዎችን በተመለከተ፣ ጋዜጠኞች ከቅርብ ጊዜ ዲጂታል የደህንነት መረጃዎች ጋር እራሳቸውን እንዲያስተዋውቁ ይመከራሉ። የሚከተለው ምክር ከሚያዚያ ወር 2013 ጀምሮ ወቅታዊ እንደሆነ ልብ ይሏል፤

ኢንተርኔት በሚዘጋበት ወቅት፤

ኢንተርኔት ከተዘጋ በኋላ፤

ሌሎች ሀብቶች፤

Exit mobile version